◐ Shell
reader mode source ↗
Jump to content
ከውክፔዲያ

የ ሙስሊሞች እምነት አላህ የ ሁሉም ፈጣሪ ማለትም ሁሉኑም የሚዳሰሱ ና የማይዳሰሱ ፍጡራኖች ካለመኖር ወደ መኖር ያመጣቸው እሱ አላህ ነው። አላህም ፍጡራንን አይመስልም ፤ በቦታም በአቅጣጫም አይገለፅም ። ምክንያቱም ቦታም አቅጣጫም ፍጡር ናቸው አልነበሩም አላህ ግን እነሱን ከመፍጠሩ በፊት ያለ እነሱ ማለትም ያለ አቅጣጫ ያለ ቦታ ነበር። ስለሆነም ፈጣሪ መቀያየር ባህሪው አይደለም አያመችበትም ፤ ለዛም ሰሀቦችም ሰለፎችም በዚህ እምነት ላይ ነበሩ። ለምሳሌ ኢማም አልይ ከሰሀቦች ኢማም አቡ ሀኒፋ ከ ሰለፎች ኢማሙ ነወውይ ከ ኸለፎች ይጠቀሳሉ።

Medallion showing "Allah" in Hagia Sophia, Istanbul, Turkey.

በእስልምና እምነት አላህ ማለት በሴማዊ ቋንቋ ውስጥ "አምልኮ የሚገባው"ፍፁም ፍጥረታትን የማይመስል፣ ከ"العرش" (ከዙፋኑ) በላይ ያለ ፣ ከፍጥረታቱ የተነጠለ፣ በአዕምሮ መንሰላሰል ሊደረስበት የማይችል ኃያል ጌታ ማለት ነው። ከነብዩ ከአደም (አ.ሰ) ጀምሮ እስከ ነብዩ ሙሃመድ (ሰ.አ.ወ) ድረስ ያሉትን በቁርአን ላይ እንደተጠቀሱት ፪፭ ሃያ አምስት እና ከዛ በላይ ያልተጠቀሱ ነብያትን የላከ አንድ እና ብቸኛ አምላክ. አላህ በቁርአን ላይ የተጠቀሱ ፱፱ (ዘጠና ዘጠኝ) ስሞች አሉት ሁሉም የሚናገሩት ስለማነነቱ እና ስለባህሪዉ ነዉ. የአላህን ለማወቅ የፈለገ ሰዉ ስሞችሁን ማስተንተን እና መረዳት ከቻለ አልላህን በመጠኑም ቢሆን ማወቅ ይችላል አሏህ መ

በቁርኣን አላህ 99 ባሕርያቱን የሚገልጹ ስሞች አሉት== አላህ ከፍጡራኑ ጋር የማይመሳሰል አስማኡል ሁስና الْأَسْمَاءُ الْحُسْنَىٰመልካም ስሞች አሉት፦ 59:24 እርሱ አላህ ፈጣሪው ከኢምንት አስገኚው ቅርጽን አሳማሪው ነው፤ ለርሱ መልካም ስሞች الْأَسْمَاءُ الْحُسْنَىٰ አሉት፤ 20:8 አላህ ከርሱ ሌላ አምላክ የለም ለርሱ መልካም የሆኑ ስሞች الْأَسْمَاءُ الْحُسْنَىٰ አሉት። 17:110 ፦አላህን ጥሩ፤ ወይም አልረሕማንን ጥሩ፤ ማንኛውንም ብትጠሩ፣ መልካም ነው፤ ለርሱ መልካም ስሞች الْأَسْمَاءُ الْحُسْنَىٰ አሉትና በላቸው፤ 7:180 ለአላህም መልካም ስሞች الْأَسْمَاءُ الْحُسْنَىٰ አሉት፤ ስትጸልዩ በርሷም ጥሩት እነዚያንም ስሞቹን የሚያጣምሙትን ተውዋቸው፤

እነዚህ 99 የባህርይ መልካም ስሞች በቁርአን የተገለጹት ናቸው እንጂ የአላህ መልካም ስሞች 99 ብቻ ናቸው ማለት አይደለም፣ ” አላህ 99 ስሞች አሉት ” ነው እንጂ ” የአላህ ስሞች 99 ናቸው ” የሚል የለም፣ ምክንያቱም ነቢያችን ራስህን በሰየምክበት፡ በመጽሐፍህም ውስጥ በጠቀስከው፡ ከፍጡሮችህም ለማንኛውም ባሳወቅከው፡ አንተ ዘንድም ብቻህን ባወቅከው ስሞችህ እለምንሀለሁ ብለዋል፦ Musnad Ahmad Book 5 number 267 It was narrated by Abdullah Ibn Mas’ud that the Prophet pbuh said: Whoever is ever afflicted by such as depression and sadness and then recites: O Allah, verily I am your servant and the son of your servant, the son of your amah (female servant), my life is in your hands, it passes in Your law, implimented as You willed, I ask of You with all the Names which is Yours, which You have named Yourself or taught anyone of your creations,or brought down in Your books, or which You have hidden by Your side in the unseen world.

በቁርአን የተገለጹ 99 ስሞች ማፈዝ፣ ማወቅ፣ ትርጉማቸውን ተረድቶ በእነዚህ ስሞች አላህን መጥራት የጀነት ያደርጋል፦ 1.ማፈዝ Sahih Bukhari, Volume 9, Book 93, Number 489: Narrated Abu Huraira: Allah’s Apostle said, “Allah has ninety-nine Names, one-hundred less one; and he who memorized them all by heart will enter Paradise.”

2.ማወቅ Sahih Bukhari, Volume 3, Book 50, Number 894: Narrated Abu Huraira: Allah’s Apostle said, “Allah has ninety-nine names, i.e. one-hundred minus one, and whoever knows them will go to Paradise.

3.ትርጉማቸውን መረዳትና መተግበር Sahih Bukhari, Volume 8, Book 75, Number 419: Narrated Abu Huraira: Allah has ninety-nine Names, i.e., one hundred minus one, and whoever believes in their meanings and acts accordingly, will enter Paradise

ነጥብ ሶስት የአላህ ስሞች የሚከተሉት ናቸው፦ 1.አል-ረሕማን፦ ሙእሚንም ካሐዲም ለሆኑ ፍጡራን እዝነቱ ሰፊና ትልቅ:: 1.1 2.አር-ረሒም፦ ለሙእሚኖች በተለየ ሁኔታ በጎ ዋይ እና አዛኝ::1.1 3.አል-መሊክ፦ በግዛቱ ያሻውን የሚፈጽም ንጉስ:: 59.23 4.አል-ቁዱስ፦ ሊታሰብ ከሚችል ባህሪ ሁሉ የጸዳ::59.23 5.አስ-ሰላም፦ ሰላሙን በፍጡራኑ ላይ የሚያሰፍን::59.23 6.አል-ሙእሚን፦ የተናገረውን የሚያጸድቅ ታማኝ::59.23 7.አል-ሙሀይሚን፦ በምሉእ ችሎታው ሁሉንም ነገር የሚቆጣጠር:: 59.23 8.አል-ዓዚዝ፦ አቻ የለሽ ሐያልና አሸናፊ:: 59.23 9.አል-ጀባር፦ ፈቃዱን በሐይል የሚፈጽም፣ ጠጋኝ እና ፈዋሽ::59.23 10.አል-ሙተከቢር፦ የልዕልና ባህሪያቱ ብቸኛ ባለቤት::59.23 11.አል-ኻሊቅ፦ ፍጡራንን በፈቃዱ የፈጠረ::59.23 12.አል-ባሪእ፦ ፍጡራንን በፈቃዱ ያስገኘ::59.23 13.አል-ሙሶዊር:- ለእያንዳንዱ ፍጡር የተለየ ቅርጽ የሰጠ::59.23 14.አል-ገፋር፦ መጥፎ ድረጊትን ይቅር የሚል::20.82 15.አል-ቀህሃር፦ አምባነገኖችን ሁሉ የሚያሸንፍ::12.39 16.አል-ወህሃብ፦ በችሮታው የሚያንበሸብሽ::3.8 17.አል-ረዛቅ፦ ሲሳዮችን የሚሰጥ::51.59 18.አል-ፈትታሕ፦ ለባሮቹ የችሮታውን ካዝናዎች የሚከፍት::32.26 19.አል-ዓሊም:- በእውቀቱ ሁሉንም ነገር ያካበበ::2.158 20.አል-ቃቢድ:- ከፍጡራኑ ለሚሻው፣ የፈለገውን ነገር የሚነሳ::2.245 21.አል-ባሲጥ :- ምስጢራቱን ለሚሻው አካል የሚያካፍል::2.245 22.አል-ኻፊድ:- ካሐድያንና ወንጀለኞችን ዝቅ የሚያደርግ::56.3 23.አር-ራፊዕ:- ወዳጆቹን ከፍ የሚያደርግ::58.11 24.አል-ሙዒዝ:- እርሱን ለሚታዘዙ አማኞች ክብር የሚለግስ::3.26 25.አል-ሙዚል:- ከሀዲያንን የሚያዋርድ::3.26 26.አስ-ሰሚዕ :- ፍጡራንን ሁሉ የሚሰማ:: 2.127 27.አል-በሲር:- ፍጡራንን ሁሉ የሚመለከት::4.58 28.አል-ሐኪም:- የነገሮችና የፍርዶች ሁሉ መመለሻ::22.69 29.አል-ዓድል:- በግዛቱ ውስጥ ነውር ወይም ጉድለት የሌለበት::6.115 30.አል-ለጢፍ:- ለባሮቹ የሚያዝን::6.103 31.አል-ኸቢር:- ግልጽም ስውርም የሆኑ ነገሮችን ሁሉ የሚያውቅ::6.18 32.አል-ሐሊም:- ለቅጣት የማይቸኩል::2.235 33.አል-ዐዚም:- ከአእምሮ ግንዛቤና ችሎታ በላይ የሆነ::2.255 34.አል-ገፉር:- ጠላቱን የሚምርና ተውበትን የሚቀበል::2.173 35.አሽ-ሸኩር :- ባሮቹን የሚመነዳ::35.30 36.አል-ዐሊይ:- ከሁሉ በላይ የኾነው::4.34 37.አል-ከቢር :- ከአልባሌ ነገሮች የጠራ::13.9 38.አል-ሐፊዝ:- ፍጡራንን ከመናጋት የሚጠብቅ::11.57 39.አል-ሙቂት:- ለፍጡራን ቀለባቸውን የሚፈጥር እና የሚያከፋፍል::4.85 40.አል-ሐሲብ:- የፍጡራንን ጉዳይ በፍትህ የሚተሳሰብ::4.86 41.አል-ጀሊል:- ልእልናውና ምሉእነቱ የላቀ::55.27 42.አል-ከሪም :- ስጦታው የማይነጥፍ::27.40 43.አር-ረቂብ:- ፍጡራንን የሚያውቅና የሚከተታተል::4.1 44.አል-ሙጂብ:- ዱዓን ተቀባይ::11.61 45.አል-ዋሲዕ :- እውቀቱ በጊዜና በቦታ የማይወሰን::2.268 46.አል-ሐኪም:- ከምሉእነቱ ጋር የሚቃረኑ ተግባራትን ከመፈጸም የጠራ::31.27 47.አል-ወዱድ:- ፍጡራኑን የሚወድ::11.90 48.አል-መጂድ:- በማንነቱም ሆነ በስራው የላቀ::11.73 49.አል-ባኢሥ:- ሙታንን ለምርመራ የሚቀሰቅስ::22.7 50.አሽ-ሸሂድ :- ግልጽም ስውርም የሆኑ ጉዳዮችን ሁሉ የሚመለከት::4.166 51.አል-ሐቅ:- ከሁሉንም ነገር የላቀ እውነት::6.62 52.አል-ወኪል:- የሁሉንም ጉዳዮች ሐላፊና ከዋኝ።3.173 53.አል-ቀዊይ:- ምንም ነገር የማይሳነው::22.40 54.አል-መቲን:- ምንም ነገር የማያሸንፈው::51.58 55.አል-ወሊይ:- በወዳጆቹ ተወዳጅ፣ የነርሱ ረዳትና አለኝታ::4.45 56.አል-ሐሚድ:- ለምስጋናና ለውዳሴ ተገቢ::14.8 57.አል-ሙሕሲ:- ጥቃቅን ጉዳዮች የማያመልጡትና ታላላቆች የማይሳኑት::72.28 58.አል-ሙብዲእ:- ፍጡራንን መጀመሪያ ካልነበሩበት ያስገኘ ፈጣሪ::10.34 59.አል-ሙዒድ:- ፍጡራንን ወደ ሞት የሚመልስ::10.34 60.አል-ሙሕይ:- የበሰበሱ አጥንቶችን ዳግመኛ ሕያው የሚያደርግ::70.158 61.አል-ሙሚት:- ነፍስን ከአካል በመነጠል የየሚያሞት::7.158 62.አል-ሐይ:- ያለና የሚኖር ሕያው::2.255 63.አል-ቀዩም:- ሁሉንም ነገር ያለ ረዳት የሚያከናውን::2.255 64.አል-ዋጅድ:- የሚፈልገውንና ያሻውን ሁሉ ማግኘት የሚችል::38.44 65.አል-ማጅድ:- የተላቀ ችሮታና በጎ ምግባር ባለቤት::85.15 66.አል-ዋሒድ:- በህላዌው አንድ የሆነ::2.163 67.አል-አሐድ:- በማንነት አንድ የሆነ::112.1 68.አስ-ሰመድ:- ጉዳዮች የሚከጀሉበት መጠጊያ::112.2 69.አል-ቃዲር:- ሁሉንም ነገር ያለ ረዳት የሚያከናውን ሁሉን ቻይ::6.65 70.አል- ሙቅተዲር:- የሻውን ነገር የሚወስን::18.45 71.አል-ሙቀዲም:- ከፍጡራን የሚሻውን የሚያስቀድም::16.61 72.አል-ሙአኽኺር:- ጠላቶቹን ከእዝነቱ በማራቅ የሚያዘገይ::71.14 73.አል-አወል:- ሁሉንም ነገር የቀደመ::57.3 74.አል-አኺር:- ፍጡራን ከጠፋ በኋላ ወደኋላ የሚቀር::57.3 75.አዝ-ዛሂር:- በምልክቶቹ፣ በተአምራቱና በአድራጎቱ ግልጽ የሆነ::57.3 76.አል-ባጢን:- ከእይታ የተሰወረ፣ ሚስጥራትን ሁሉ አዋቂ:: 57.3 77.አል-ዋሊ:- የነገሮች ባለቤት፣ በችሮታው ውለታ የሚውል።13.11 78.አል-ሙተዓል:- ደረጃው ከፍ ያለ፣ በክብሩና በሕልውናው የላቀ::13.9 79.አል-በር:- ለለመኑት ቸር::52.28 80.አት-ተዋብ:- ከባሮቹ ተውበትን ንስሃን የሚቀበል::2.128 81.አል-ሙንተቂም:- ብቀላው የሚፈራ::32.22 82.አል-ዓፍዉ:- ወንጀልን የሚያብስ::4.99 83.አር-ረኡፉ :- ለባሮቹ በጣም አዛኝ::3.30 84.ማሊከል ሙልክ:- በንግስናው የፈለገውን የሚያደርግ::3.26 85.ዙልጀላሊ ወልኢክራም:- የልእልናዎችና የልቅናዎች ሁሉ ባለቤት::55.27 86.አል-ሙቅሲጥ:- ፍትሕ አስፋኝ ፍትሐዊ::7.29 87.አል-ጃሚዕ:- ሁሉ የሰበሰበ ሰብሳቢ::3.9 88.አል-ገንይ:- አንዳች ነገር የማይከጅል ሐብታም::3.97 89.አል-ሙግኒ:- ከባሮቹ ለሚሻው ሰው የሚሰጥ::9.28 90.አል-ማኒዕ:- ባሮቹን ለመጠበቅ የሚያቅብ::67.21 91.አድ-ዷር:- ከባሮቹ የሚሻውን የሚጎዳ::6.17 92.አን-ናፊዕ:- የመጥቀም ባለቤት::30.37 93.አን-ኑር:- የእውነተኞችን ልቦናዎች የሚያበራ::24.35 94.አል-ሃዲ:- ሁሉንም ነገር የፈጠረና የመራ::22.54 .95.አል-በዲዕ:- ጥበበ-ረቂቅ ፈጣሪ::2.117 96.አል-ባቂ:- ዝንተ ዓለም የሚኖር::55.27 97.አል-ዋሪስ:- ፍጡራንን ሁሉ ወራሽ::15.23 98.አር-ረሺድ:- የሚመራ አመላካች::2.256 99.አስ-ሰቡር:- የሚታገስ፣ የማይቸኩል። 2.153